1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኅብረተ ሰብሰሜን አሜሪካ

ግድያ በሊዊስተን አሜሪካ፤ የአሜሪካን አዲስ የምክር ቤት አፈ ጉባኤ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 15 2016

በዩናይትድ ስቴትስዋ ሊዊስተን ከተማ በሁለት ስፍራዎች አንድ ታጣቂ በተከፈተው ተኩስ ከ22 ያላነሱ ሰዎች ሞቱ፤ ሀምሳ የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ ቆሰሉ። ተጠርጣሪው ዛሬም በግዛቷና በፌደራል ኃይሎች እየተፈለገ ነው። በሌላ በኩል ለ22ቀናት ያለ አፈጉባኤና ያለ ስራ የቆየው የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትናንትናው እለትአዲስ አፈ ጉባኤ መርጧል።

https://p.dw.com/p/4Y4LF
Neuer Vorsitzender US-Repräsentantenhaus Mike Johnson
ምስል ALEX WONG/Getty Images/AFP

የሌዊስተን ዩናይትድ ስቴትሱ ግድያና አዲስ የምክር ቤት አፈ ጉባኤ መመረጣቸው

በዩናይትድ ስቴትስዋ የሜይን ግዛት ውስጥ በምትገኘው ሊዊስተን ከተማ በሁለት ስፍራዎች በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ ከ22 ያላነሱ ሰዎች ሞቱ፤ ሀምሳ የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ ቆሰሉ። ተጠርጣሪው እስከአሁን አልተያዘም።በዩናይትድ ስቴትስ ወንጀል መስፋፋቱ ዛሬም በግዛቷና በፌደራል ኃይሎች እየተፈለገ ነው። በሌላ በኩል በትናንትናው እለት ለ22ቀናት ያለ አፈጉባኤና ያለ ስራ የቆየው የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዲስ አፈ ጉባኤ መርጧል። ስለ ሁለቱ የትናንት ማምሻ ክስተቶች የዋሽንግተን ዲሲ ዘጋቢያችንን አበበ ፈለቀን አነጋግረናል።
አበበ ፈለቀ 
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ