የኮሮና መከላከያ ክትባት በትግራይ
ማክሰኞ፣ ግንቦት 24 2013ማስታወቂያ
ትግራይ ክልል ዉስጥ በሚደረገዉ ዉጊያና ግጭት ምክንያት ተዘንግቶ የነበረዉ የኮሮና ተሕዋሲን የመከላከል አገልግሎትና ጥንቃቄ ቀስበቀስ እያንሰራራ መሆኑን የክልሉ የጤና ባለሙያዎች አስታወቁ።ሐኪሞችና ሌሎች የጤና ባለሙያዎች እንደሚሉት የኮሮና ተሕዋሲ መከላከያ ክትባትም ለተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች እየተሰጠ ነዉ።ሕዝቡ ተሕዋሲዉን ለመከላከል የሚያደርገዉ ጥንቃቄ በመላላቱ ተሕዋሲዉ በተለይ በየመጠለያ ጣቢዎች በፍጥነት እየተሰራጨ መሆኑን ተፈናቃዮች አስታዉቀዋል።
ሚሊዮን ኃይለስላሴ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ