1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስለኬንያ ምርጫ የኢትዮጵያውያን ታዛቢዎች አስተያየት

ዓርብ፣ ነሐሴ 6 2014

እንደ ዶ/ር ዳኒኤል ትዝብት በእለተ ምርጫው በነበረው ሂደት ግን ነጻ እና ፍጹም ሰላማዊ የመራጮች ተሳትፎ ተስተውሏል፡፡ በኬንያ ውስጥ በሁለት የምርጫ ዘመን የተገደበው የፕሬዝዳንትነት ሚና መከበሩ እና እስካሁን ሶስት ፕሬዝዳንቶች ስልጣናቸውን ለአሸናፊ በሰላም ማስረከባቸውም ለአፍሪካም ጭምር መልካም ልምድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

https://p.dw.com/p/4FT66
Kenia Nairobi Wahlen Wahllokal
ምስል Thomas Mukoya/REUTERS

ስለኬንያ ምርጫ የኢትዮጵያውያን ታዛቢዎች አስተያየት

ኬንያ ባሳለፍነው ማክሰኞ ባከናወነችው ብሔራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃለማሪያም ደሳለኝ እና የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ ሌሎች ፖለቲከኞች እና የሲቪክ ተቋማት ተወካዮች በታዛቢነት ተሳትፈው ነበር፡፡
ዶይቼ ቬለ በምርጫው በታዛቢነት ከተሳተፉት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና የኢትየጶጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር (ኢሰመኮ) ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ትዝብታቸውን ተጋርቷል፡፡ እኚህ ሁለቱም ታዛቢዎች ዋና መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ባደረገው የሲቪል ተቋም አመቻችነትና ጋባዥነት ነበር በዓለማቀፍ የምርጫ ታዛቢነት የተሳተፉት፡፡
የኦፌኮው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ የደቡብ አፍሪካው የሲቪክ ተቋም በስምንት ቡድኖች ካሰማራቸው 40 ታዛቢዎች አንዱ ሆነው ነበር በአራት ቡድን በሞምባሳ የምርጫ ክልል የተሰማሩት፡፡ ፕሮፌሰር መረራ እንደሚሉት በዚያው እሳቸው በታዘቡበት የምርጫ ጣቢያ እና ሌላው ኪሱሙ በሚባል ግዛት የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት መሪው ራይላ ኦዲንጋ ሲመሩ እንደ ሪፍት ቫሊ ባሉ ግዛት ደግሞ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ዊሊያም ሩቶ በለስ ሳይቀናቸው እንዳልቀረ አመልክተዋል፡፡
የኢሰመኮ ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለም ከአራት ቡድናቸው ጋር በመሆን በአራት የምርጫ ክልሎች ነበር ሂደቱን የታዘቡት፡፡ ናይሮቢ፣ ኪሱሙ፣ ሞምባሳ እና ኤልዶሬ ምርጫውን ከታዘቡባቸው አከባቢዎች ናቸው፡፡ ስድስት አይነት ምርጫዎች ከአገር መሪነት እስከ የአከባቢ ምክር ቤት አባልነት በተከናወነበት በባለፈው ማክሰኞው ምርጫ ፕሬዝዳንታዊ ፉክክሩ ልዩ ትኩረት መሳቡንም አንስተውልናል፡፡ ቀዝቀዝ ያለ የተመዝጋቢዎች ተሳትፎ ታይቶበታል የተባለው የኬንያው ምርጫ ከተመዘገቡት 22 ሚሊየን መራጮች ገደማ ከ60 በመቶ ያልበለጡ ብቻ ወጥተው መምረጣቸው ነው የሚነገረው፡፡
እንደ ዶ/ር ዳኒኤል ትዝብት በእለተ ምርጫው በነበረው ሂደት ግን ነጻ እና ፍጹም ሰላማዊ የመራጮች ተሳትፎ ተስተውሏል፡፡ በኬንያ ውስጥ በሁለት የምርጫ ዘመን የተገደበው የፕሬዝዳንትነት ስልጣን መከበሩ እና እስካሁን ሶስት ፕሬዝዳንቶች ስልጣናቸውን ለአሸናፊው በሰላም ማስረከባቸውም ለአፍሪካም ጭምር መልካም ልምድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ፕሮፌሰር መረራ በፊናቸው የታዘቡትን ሲያጋሩን፡ መራጮች የተለየ አማራጭ ብለው ያሰቡት ተወዳዳሪዎች በምርጫው መሳተፋቸው ተሳትፎያቸውን ለማቀዘቀዙ ምክኒያት ሳይሆን እንዳልቀረ ነግረውናል፡፡ የኬንያ ተቀናቃኝ ፓርቲ ዋነኛው ሰው ራይዳ ኦዲንጋ ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የሚያውቁ ሲሆን በተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ይደገፋሉ፡፡ ዊሊያም ሩቶም ቢሆኑ የአሁኑ ምክትል ፕሬዝዳንት እንደመሆናቸው ኬንያውያን ከአሁኑ ምርጫ ብዙም ለውጥ ላይጠብቁ እንደሚችሉ ፕሬፌሰር መረራ ትዝብታቸውን አጋርተውናል፡፡
በማክሰኞው የኬኒያው ምርጫ ኬንያውያኑ መርጠው ከፍተኛ ተወዳዳሪነት ካሳዩት ምክትል ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የኬንያ የተቃውሞ ፖለቲካ ዋነኛ ሰው ራይላ ኦዲንጋ፤ ማናቸው 5ኛው ፕሬዝዳንት ይሆናል የሚለውን አሁንም እየተጠባበቁ ነው፡፡

Daniel Bekele | Leiter der äthiopischen Menschenrechtskommission
ምስል EDUARDO SOTERAS/AFP/Getty Images
Pro Merera Gudina vorsitzender OFECO
ምስል DW/S. Wegayehu

ስዩም ጌቱ

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

እሸቴ በቀለ