በጀርመን በቀኝ ጽንፈኞች ላይ የተጠናከረው ተቃውሞ
ማክሰኞ፣ ጥር 14 2016በጀርመን በቀኝ ጽንፈኞች ላይ የተጠናከረው ተቃውሞ
ጀርመናውያን ሰሞኑን በሚያካሂዷቸው የተቃውሞ ሰልፎች ከወትሮው በተለየ በቀኝ ጽንፈኞች ላይ ቁጣቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከአርብ እስከ እሁድ ትላላቅ የሚባሉትን ከተሞች በርሊን ሙኒክና ኮሎኝን ጨምሮ ቢያንስ አንድ መቶ በሚሆኑ አካባቢዎች «አማራጭ ለጀርመን» የተባለውን ቀኝ ጽንፈኛ ፓርቲንና መሰሎቹን በመቃወም እስከ 1.4 ሚሊዮን የተገመተ አደባባይ ወጥቷል።በርሊን የቀኝ ጽንፈኞች ተቃውሞና የሃገሪቱ መሪዎች ቁጣ
ይህን ያህል ቁጥር ያለው ህዝብ በገፍ አደባባይ ወጥቶ መቃወም የጀመረው «ኮሬክቲቭ» የተባለው በምርመራ ጋዜጠኝነት ላይ የተሰማራው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ባለፈው ኅዳር ፖስትዳም በተባለው ከተማ በጀርመን ምክር ቤት ውስጥ መቀመጫ ያለው ተቃዋሚው አማራጭ ለጀርመን የተባለው ፓርቲ ከሌሎች ቀኝ ጽንፈኞች ጋር የውጭ ዝርያ ያላቸውን ሰዎች እንዴት ከጀርመን እንደሚያባርሩ በድብቅ የተነጋገሩበትን እቅድ ካጋለጠ በኋላ ነው። ጀርመን የተማሩትና የሚሰሩት የፖለቲካ ሳይንስና የሕግ ምሁር ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ቀኝ ጽንፈኞቹ በድብቅ በተነጋገሩበት ሰነድ መሠረት ከጀርመን ለማባረር የያቀዱት መሰረታቸው የውጭ የሆነ የጀርመን ነዋሪዎችና ዜጎች ቁጥር በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ነው.።እነዚህ ቡድኖች እቅዱን ተግባራዊ የሚያደርጉበትን መንገድም ጭምር በሰነዱ አካተዋል።
ህዝቡ ቁጣውን በገለጸባቸው ሰልፎች የተሰጡ አስተያየቶች
በዚህ የቀኝ ጽንፈኞች እቅድ የተቆጣው ህዝብ በየሚገኝባቸው ከተማዎች ጊዜ ሳያጠፋ ነበር ግልብጥ ብሎ በመውጣት በአደባባይ ሰልፍ ተቃውሞውን ማሰማት የጀመረው። በምዕራብ ጀርመንዋ በኮሎኝ ከተማ በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የተገኙት ሽቴፋን ካልሽ ቀኝ ጽንፈኞች ገደቡን ጥሰው ማለፍ የጀመሩት አሁን አይደለም ይላሉ። «በኔ አመለካከት መስመሩ ከተጣሰ ብዙ ጊዜ ሆኖታል። ሆኖም በተለይ ፖለቲካው ፣በጉዳዩ ላይ ሁሌም በጣም ዝም እንዳለ ነው። አሁን ደግሞ ሁሉም ነገር አንድ ላይ በፍጥነት እየመጣ ነው። «ኮሬክቲቭ» የተባለው የምርመራ ጋዜጠኝነት የሚያካሂደው ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት ነገሮች በተሳሳተ አቅጣጫ እየሄዱ መሆኑ ግልጽ ነው። ኬምኒትስ ቀኝ ጽንፈኞች እና ተቃዋሚዎቻቸው
ስለዚህ ሁሉም አሁን አደባባይ መውጣት አለበት።ይህ ደግሞ እስከዛሬ በንቃት ተቃውሞአቸውን ለሚያሰሙት ሳይሆን እስካሁን ዝምታን ለመረጡት ነው።» እሁድ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት በበርሊኑ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የተካፈሉት የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አማካሪ ጀራልድ አንገረር ሰልፍ የወጡት ጊዜው አሁን ነው ብለው ስላሰቡ መሆኑን ተናግረዋል። «ሁሉንም ነገር ስከታተል ነበርና ቀኝ ጽንፈኞችን ተቃውሞ አደባባይ መውጫ፣ ፊቴንም፣መኖሬንም በአደባባይ ማሳያው ጊዜው አሁን ነው ብዬ ስላሰብኩ ነው።»
ሊዲያ ሽቴፈን ሀገን የተባሉት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሞያ ጉዳዩን ንቆ ይተው የነበረው ህዝብ አደባባይ መውጣቱን አድንቀዋል። «ነገሮች ወዴት እንደሚሄዱ የምናይ ይሆናል። ግን በስተመጨረሻ አንድ ነገር መደረጉ ፣ዝምታን መርጦ የቆየው ብዙሀኑ እንደቀድሞው ዝም ብሎ አለመቅረቱ ጥሩ ነው» እንደሽቴፈንሀገን ሁሉ ሌላዋ ሰልፈኛ ኡተ ራውትንበርግም የጽንፈኞች እንቅስቃሴ እስካሁን ችላ ተብሎ መቆየቱን ያምናሉ።« እንደሚመስለኝ ወደ ቀኝ ማዘንበሉ ጎልቶ በሚታይ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተስፋፋ ነው። እኔ እንደምለው እዚህ ያለነው የተቀረነው እኛ ፣ጉዳዩ የትም አይደርስም ፤ እነዚያ ጥቂቶቹ የሚያስቡት ትክክል አይደለም ብለን ነበር። ሆኖም የነርሱ አመለካከት ከሚታሰበው በላይ ተዛምቷል።»የዞሊንገኑ የቀኝ ጽንፈኞች ጥቃት 30ኛ ዓመት
ከሰልፎቹ ምን ይጠበቃል?
አቶ ሀብተአብ ኢያሱ ጀርመን ሲኖሩ ከ30 ዓመት በላይ ሆኗቸዋል ።ከፍተኛ ትምሕርታቸውን የተከታተሉትም የሚሰሩትም እዚሁ ጀርመን ነው። ህዝቡ ዓይንህ ላፈር ያለውን «አማራጭ ለጀርመን» ፓርቲ በዴሞክራሲ ስም ተደብቆ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ ነው የሚሉት። ከ10 ዓመት በፊት የተመሰረተው የአማራጭ ለጀርመን ፓርቲ ደጋፊዎች ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ፓርቲው በአጭር ጊዜ ውስጥ የፌደራሉን ምክርቤት ጨምሮ በተለያዩ የጀርመን ግዛቶች መቀመጫዎች አሉት። አቶ ሀብተአብ እንደሚሉት ግን የአሁኑ ተቃውሞ ከዚህ ቀደምና አሁንም ፓርቲውን አሳንሰው ለሚያዩት የተለያዩ መልዕክቶችን ያስተላለፈ ነው። ከመካከላቸው ከዚህ ቀደም የፓርቲውን እንቅስቃሴዎች ችላ ይሉ የነበሩ ሰዎችን ማንቃት ይገኝንበታል። ምርጫ የማይሄደው ህዝብ ምርጫ እንዲወጣ ይገፋፋል ብለው ይጠብቃሉ።
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ